ጠበቆች ሙያዊ የሚጠይቀውን ስነ ምግባር ጠብቀው በመስራት የፍትህ ስርዓቱን የማገዝና የህዝብን ጥቅም የማስከበር ኃላፊነት አለባቸው፡-
የምዕራብጎጃም ዞን ፍትህ መምሪያ ኃላፊ አቶ እሱባለው መኮንን
መምሪያው ከምዕራብ ጎጃም ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ጋር በመተባበር ከፍኖተ ሰላም ከተማና አካባቢው ከሚገኙ ጠበቆች ጋር በፍትህ አስተዳደሩ ጠበቆች ያላቸውን ሚና ለማሳደግ ያለመ የምክክር መድረክ በፍኖተ ሰላም ከተማ እየተካሄደ ነው።
የምዕራብ ጎጃም ዞን ፍትህ መምሪያ ኃላፊ አቶ እሱባለው መኮንን ጠበቆች የፍትህ ስርዓቱን በማሳለጥ ህዝብ የሚያምነው የፍትህ አስተዳደር እንዲገነባ በማስቻል በኩል የማይተካ ሚና እንዳላቸው ገልጸዋል።
የጥብቅ ሙያ ትልቅ ክብር የሚሰጠውና ጥብቅ የሙያ ስነ ምግባር ጠብቆ የሚሰራ ነው ያሉት አቶ እሱባለው ጠበቆች ለሙያቸውና ህሌናቸው ተገዥ በመሆን የህዝብን ጥቅም የማክበርና የማስከበር ኃላፊንታቸውን ሊወጡ ይገባል ብለዋል።
የጥብቅና ስራ ግለሰቦች በእውቀት ማነስ ምክንያት መብትና ጥቅሞቻቸው እንዳይጣስና አለመግባባቶችን በህግ የመፍታት ባህል እንዲጎለብት የማይተካ ሚና የሚወጡ በመሆኑ ጠበቆች ኃላፊነታቸውን በአግባቡ ሊወጡ ይገባልም ነው ያሉት።
የምዕራብ ጎጃም ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ አባይነህ ካሴ በበኩላቸው የፍትህና ዳኝነት ስርዓቱ በቅብብሎሽ የሚሰራ በመሆኑ ጠበቆች ሙያቸውን አክብረው በመስራት የህዝቡን መብትና ጥቅም ለማስጠበቅ የድርሻቸውን ሊወጡ ይገባል ብለዋል።
ወደ ፍርድ ቤት የሚመጡ ክርክሮች በአብዛኛው በጠበቆች አልፈው የሚመጡ በመሆናቸው ጠበቆች የጥብቅና ስነ ምግባርን ጠብቆው ባለ ጉዳዮችን ማገልገል እንደሚጠበቅባቸውም ነው የገለጹት። Source:- West Gojjam Communication
የምዕራብጎጃም ዞን ፍትህ መምሪያ ኃላፊ አቶ እሱባለው መኮንን
መምሪያው ከምዕራብ ጎጃም ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ጋር በመተባበር ከፍኖተ ሰላም ከተማና አካባቢው ከሚገኙ ጠበቆች ጋር በፍትህ አስተዳደሩ ጠበቆች ያላቸውን ሚና ለማሳደግ ያለመ የምክክር መድረክ በፍኖተ ሰላም ከተማ እየተካሄደ ነው።
የምዕራብ ጎጃም ዞን ፍትህ መምሪያ ኃላፊ አቶ እሱባለው መኮንን ጠበቆች የፍትህ ስርዓቱን በማሳለጥ ህዝብ የሚያምነው የፍትህ አስተዳደር እንዲገነባ በማስቻል በኩል የማይተካ ሚና እንዳላቸው ገልጸዋል።
የጥብቅ ሙያ ትልቅ ክብር የሚሰጠውና ጥብቅ የሙያ ስነ ምግባር ጠብቆ የሚሰራ ነው ያሉት አቶ እሱባለው ጠበቆች ለሙያቸውና ህሌናቸው ተገዥ በመሆን የህዝብን ጥቅም የማክበርና የማስከበር ኃላፊንታቸውን ሊወጡ ይገባል ብለዋል።
የጥብቅና ስራ ግለሰቦች በእውቀት ማነስ ምክንያት መብትና ጥቅሞቻቸው እንዳይጣስና አለመግባባቶችን በህግ የመፍታት ባህል እንዲጎለብት የማይተካ ሚና የሚወጡ በመሆኑ ጠበቆች ኃላፊነታቸውን በአግባቡ ሊወጡ ይገባልም ነው ያሉት።
የምዕራብ ጎጃም ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ አባይነህ ካሴ በበኩላቸው የፍትህና ዳኝነት ስርዓቱ በቅብብሎሽ የሚሰራ በመሆኑ ጠበቆች ሙያቸውን አክብረው በመስራት የህዝቡን መብትና ጥቅም ለማስጠበቅ የድርሻቸውን ሊወጡ ይገባል ብለዋል።
ወደ ፍርድ ቤት የሚመጡ ክርክሮች በአብዛኛው በጠበቆች አልፈው የሚመጡ በመሆናቸው ጠበቆች የጥብቅና ስነ ምግባርን ጠብቆው ባለ ጉዳዮችን ማገልገል እንደሚጠበቅባቸውም ነው የገለጹት። Source:- West Gojjam Communication